አርትስ 18/04/2011rnrnጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ የሕግና ፍትህ አማካሪ ጉባዔ አባላትን ያመሰገኑት ትናንት በፅ/ቤታቸው ከአባላቱ ጋር በተወያዩበት ጊዜ ነው።rnrnጠቅላይ ሚኒስትሩ ምስጋናቸውን የቸሩት የጉባዔው አባላት የሕግ ማሻሻያዎችን በመከለስና ምክረ ሃሳብ በመስጠት ላደረጉት የነፃ አገልግሎትነው።rnrnከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት በተገኘው መረጃ ጠቅላይ ሚኒስትር ዓቢይ አህመድ እንደ የፀረ-ሽብርና የሲቪል ማህበራት ባሉ የሕግማዕቀፎች ላይ የሚደረጉ ማሻሻያዎች፤ የሕግ የበላይነትን ሳይጋፉ የዜጎችን መብትና ነፃነት እንዲያስከብሩ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።rnrnየሕግና ፍትህ አማካሪ ጉባዔ ከአራት ወራት በፊት በፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ መዋቀሩ የሚታወስ ሲሆን በተለያዩ የሀገሪቱ ህጎች ላይ ማሻሻያ እንዲደረግባቸው እየተንቀሳቀሱ ይገኛል።መረጃዉን ያገኘነዉ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ነዉ፡፡






