Arts TVArts TV
← NewsLegal

አንጎላ ሙስናን ለመዋጋት የተባበሩት መንግስታት ይርዳኝ እያለች ነው

Arts TV · ኦክቶ 30 2018

አንጎላ ሙስናን ለመዋጋት የተባበሩት መንግስታት ይርዳኝ እያለች ነውr

አርትስ 20/02.2018

r

የሃገሪቱ ሃብት ተመዝብሮ  በውጭ ሃገራት ተከማችቷል የሚሉት የአንጎላ ባለስልጣናት ሙስናን ለመዋጋት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲረዳቸው መማጸናቸውን አምነዋል።

r

r

ጆርናል ዲ አንጎላ የተባለውን የአንጎላ ጋዜጣ ጠቅሶ ዘ ኢስት አፍሪካን እንደዘገበው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከዚህ ቀደም ድንበር ዘለል ሙስናን ለመከታተል የተቋቋመውን የሃገሪቱን ጠቅላይ ዐቃቢህግ ቢሮ ሲደግፍ ነበር።

r

r

አሁንም ተዘርፎ በውጭ ሃገር የተከማቸ ሃብቴን ለማስመለስ የድርጅቱ ድጋፍ ያስፈልገኛል እያለች ነው አንጎላ  ።

r

r

የአንጎላ ብሄራዊ መጠባበቂያ ባንክ ገዢ የሆኑት ሚስተር ጆሴ ዴ ሊማ ማሳኖ እንዳረጋገጡት ከ30 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር በላይ የሚሆን የአንጎላ ሃብት በውጭ ሃገራት ተከማችቷል።

r

r

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማኑኤል አውግስቶ ደግሞ ባለፈው ወር ከአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት ጋር ተገናኝተው የተሰረቀውን የአንጎላን  ሃብት ለማስመለስ ድጋፍ መጠየቃቸውንአረጋግጠዋል።

More in Legal