Arts TVArts TV
← NewsLegal

አንድ ግለሰብ በተጭበረበረ ቼክ 14 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር ሊያወጣ ሲል ተያዘ

Arts TV · ኖቬም 19 2018

አርትስ 10/03/2011rnrnተጠርጣሪው አቶ ገመቹ ጫላ በሚል ስም  ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሻላ ቅርንጫፍ  ባለፈው አርብ የባንክ ሂሳብ የከፈተ ነው።rnrnዛሬም ወደ ባንኩ ቅርንጫፍ በማምራት በተጭበረበረ የአምበሳ አውቶብስ ቼክ 14 ሚሊዮን  724 ሺህ ብር  በማውጣት አርብ ዕለት ወደ ከፈተው የባንክ ሂሳብ ለማዛወር ሲል ነው በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ክትትል ተደርጎበትመያዙን ፋና የዘገበው ።rnrnተጠርጣሪው በሰዓቱ ለባንኩ ቅርንጫፍ የደንበኞች አገልግሎት ኃላፊ 1 ሚሊዮን ብር ጉርሻ በማቅረብ እንዲፈፀምለት ለማግባባት ሞክሮም እንደነበር ተመልክቷል።

More in Legal