በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጠገዴ ወረዳ ተቀብሮ የነበረ የእጅ ቦምብ ፈንድቶ የሁለት ህፃናት ህይወት አለፈ
rnአርትስ 25/03/2011rnፓሊስ እንዳስታወቀዉ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጠገዴ ወረዳ ተቀብሮ የነበረ የእጅ ቦምብ ፈንድቶ የሁለት ህፃናትን ህይወት እንዲያልፍና በስድስቱ ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ እንዲደርስ አድርጓል ብሏል፡፡rnrnየዞኑ ፓሊስ መመሪያ ሀላፊ ኮማንደር እንየው ዘውዴ፥ ቦምቡ በጠገዴ ወረዳ ቡሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አቅረቢያ በግምት በ350 ሜትር ርቀት የተከሰተ ነው ብለዋል።rnrnሀላፊው ኤፍ 1 የተባለ የእጅ ቦንብ ህፃናት ተማሪዎች ዋርካ ስር ሆነው እያነበቡ በነበረበት ወቅት መፈንዳቱንና ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል።