Arts TVArts TV
← NewsAfrica

32ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ  የካቲት 11 ይጀመራል

Arts TV · ፌብ 1 2019

<strong>32ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ  የካቲት 11 እንደሚጀመር የውጭ ጉዳይ  ሚኒስቴር ገልጿል፡፡</strong>rnrnየውጭ ጉዳይ  ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው  ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደተናገሩት ከየካቲት 7 እስከ 8 የሚኒስትሮች ስብሰባ የሚካሄድ መሆኑን ገልፀው  ከየካቲት 10 እስከ 11 ድረስ  ደግሞ የመሪዎቹ ስብሰባ ይቀጥላል ብለዋል፡፡rnrnበ32ኛው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ወቅት የአፍሪካ ህብረት ተቋማዊ ሪፎርምን በተመለከተ በጥልቀት ውይይት የሚደረግበት እና  የወቅቱ የህብረቱ ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜን ጨምሮ ዋና ፀሃፊው ሙሳ ፋቂ መሀመት የአፈፃፀም ሪፖርታቸውን የሚያቀርቡበት ነው ተብሏል።rnrnበጉባኤው ላይ ከሌሎች ጊዜያቶች በተለየ የአፍሪካ እና የኢትዮጵያ አርቲስቶች አፍሪካን በሚያጎላ መልኩ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡበት እና አፍሪካዊ ትዕይንቶች የሚቀርቡበት እንዲሆን ቅድመ ዝግጅት መደረጉንም ሀላፊው ተናግረዋል፡፡rnrn&nbsp;rnrn&nbsp;rnrn&nbsp;

More in Africa