የመድሀኒት እጥረትን በቋሚነት ለመፍታት የሚያስችል የኤሌክትሮኒክ የመድሀኒት ምዝገባ ና ቁጥጥር ሥርዓት መጀመሩን ባለሥልጣኑ አስታወቀ፡፡rnrnበኤሌክትሮኒክስ የመድሀኒት ምዝገባ ና ቁጥጥር ሥርዓት መጀመሩ ይፋ ሲደረግ የተገኙት የጤና ሚኒስትሩ ዶ/ር አሚር አማን የፌዴራል ምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጠን የሚሰጣቸዉን አገልግሎቶች እጅግ ወሳኝ በመሆናቸዉ አስተማማኝ መሆን እንደሚጠበቅባቸዉ ተናግረዋል ፡፡rnrnዶክተር አሚር መስሪያቤታቸዉ ሊተገብራቸዉ በእቅድ ከያዛቸዉ አጀንዳዎች መካከል አንዱ የሆነዉ የመረጃ አብዮት ነዉ በኤሌክትሮኒክ የመቆጣጠሪያ ሥርዓት የሚከናወኑ የመድሀኒት ምዝገባ ና ቁጥጥር ሥርዓት ደግሞ ለዚህ ወሳኝ ነዉ ብለዋል፡፡rnrnየፌዴራል የምግብና መደሀኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሪት ሄራን ገርባ በበኩላቸዉ በሀገራችን የሚታየዉን የመድሀኒት እጥረት በቋሚነት ለመፍታት እንዲቻል ፤ የመድሀኒት ምዝገባ ሥርዓቱን የተቀላጠፈና ምቹ ለማድረግ መሠረታዊ ለዉጥ ማምጣት አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ ይህ ዘመናዊ የአሠራር ሥርዓት ተዘርግቷል ብለዋል፡፡rnrnየኤሌክትሮኒክ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቱ ህገወጥ መድሀኒቶችን የመለየትና የማወቅ ፣የመድሀኒት ግዥን፣የምግብና መድሀኒት ብቃት ማረጋገጫን ማከናወን፣ የምግብ ምዝገባ እንዲሁም የመድሀኒት ምዝገባን ማከናወን ሲሆን ሁሉንም አገልግሎቶች በቀላሉ ካሉበት ቦታ በመሆን በኦንላይን ማከናወን ያስችላል፡፡rnrn rnrn
← NewsHealth
የመድሀኒት እጥረትን በቋሚነት ለመፍታት የሚያስችል የኤሌክትሮኒክ የመድሀኒት ምዝገባ ና ቁጥጥር ሥርዓት መጀመሩን ባለሥልጣኑ አስታወቀ፡፡
Arts TV · ፌብ 28 2019






