Arts TVArts TV
← NewsAfrica

የመምህራን አገልግሎት ኮሚሽን ሊቋቋም ነው፡፡

Arts TV · ኤፕሪ 9 2019

የመምህራን አገልግሎት ኮሚሽን ሊቋቋም ነው፡፡

የመምህራን አገልግሎት ኮሚሽን ሊቋቋም ነው፡፡rnrnበመምህራን ጉዳዮች ላይ የሚሰራ የመምህራን አገልግሎት ኮሚሽን ሊቋቋም መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።rnrnየኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር ፕሬዚዳንት ዶክተር ዮሃንስ በንቲ የትምህርትን ጥራት ለማሻሻል የትምህርት ሙያተኛውን ኑሮ ማሻሻል እንደሚገባ ገልጸዋል።rnrnለዚህም ዘርፉን ለመምራት ከሲቪል ሰርቪስ የተለየና ተጠሪነቱም ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሆነ ኮሚሽን እንዲቋቋም መጠየቃቸውን ነው የተናገሩት።rnrnበሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የትምህርትና ስልጠና ፍኖተ ካርታ ዝግጅትና ትግበራ ሴክሬታሪያት ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ፥ ፍኖተ ካርታው አጠቃላይ የትምህርትና ስልጠና ስርዓቱን እንደሚፈትሽ ነው ተናግረዋል።rnrnኮሚሽኑ በጥናት ላይ ተመስርቶ የመምህራንን ጥቅማ ጥቅም ለማስከበር በዝርዝር እንደሚሰራ ጠቅሰው፥ ኮሚሽኑን ለማቋቋም የህግ ማዕቀፎች እየተዘጋጁ መሆኑንም ገልፀዋል።rnrnኢዜአ እንደዘገበው የትምህርት ማኅበረሰቡን አደረጃጀት፣ ስነ ምግባር እና ጥቅማ ጥቅሙን በሚመለከት ነጻ በሆነ አካል ተጠንቶ ከመቋቋሙ አስቀድሞ በሚመለከታቸው አካላት ሀሳብ ይሰጥበታል፡፡rnrn 

More in Africa