Arts TVArts TV
← NewsHealth

በአርሲ ዩኒቨርሲቲ በኢንተርን ሀኪሞች ላይ የደረሰውንጉዳት እንዳሳዘነዉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

Arts TV · ኤፕሪ 18 2019

በአርሲ ዩኒቨርሲቲ በኢንተርን ሀኪሞች ላይ የደረሰውንጉዳት እንዳሳዘነዉ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ፡፡rnrnበአገራችን እየተካሄደ ባለው ሁሉን አቀፍ ሪፎርም ሀሳብን በነጻነት ከመግለጽ ጀምሮ የተለያዩ ሰብአዊና ህጋዊ መብቶች እንዲከበሩ መንግስት ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ያላሰለሰ ጥረት እያደረገ ይገኛል::rnrnየህክምና ባለሙያዎች እንደማንኛውም ግለሰብና ባለሙያ ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ የማቅረብ መብት እንዳላቸው በጽኑ ይታመናል ብሏል የጤና ሚኒስቴር ፡፡rnrnየጤና ሚኒስትሩ በትላንትናዉ  እለት  በአርሲ ዩኒቨርስቲ ኢንተርን ሀኪሞች ጥያቄዎቻቸውን በሰላማዊ መንገድ ለዩኒቨርስቲው አመራሮች ለማቅረብ በወጡበት ወቅት በአከባቢው የሚገኘው ስርዓት አስከባሪ የኃይል እርምጃ በመውሰድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ከደረሰን ሪፖርት መረዳት ተችሏል  ብሏል::rnrnበደረሰው ጉዳት የጤና ሚኒስቴር እጅጉን ያዘነ ስሆን ይህንን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተለ ይገኛል::rnrnጉዳቱን ያደረሱ አካላትም በአስቸኳይ አስፈላጊው ማጣራት ተደርጎ ተገቢው ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ከሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን እየሰራ ይገኛል ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡

More in Health