Arts TVArts TV
← NewsEconomy

1መቶ 80 ሺህ የአሜሪካ ዶላርን  ጨምሮ የ3 ሀገራት የዉጭ ገንዘብ  በህገወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ ሲል ተያዘ፡፡

Arts TV · ኤፕሪ 15 2019

1መቶ 80 ሺህ የአሜሪካ ዶላርን  ጨምሮ የ3 ሀገራት የዉጭ ገንዘብ  በህገወጥ መንገድ ከሀገር ሊወጣ ሲል ተያዘ፡፡rnrnበቶጎ ጫሌ የፍተሻ ጣቢያ የተያዘ ገንዘብ ወደ ብር ሲቀየር ከ8 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ገቢዎች ሚኒስቴር ገልጿል፡፡rnrnበዛሬዉ ዕለት ኮድ 3 04867 ድሬ የሆነ ተሽከርካሪ ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ በቶጎ ጫሌ ኬላ 182 ሺህ 247 የአሜሪካን ዶላር ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲቀየር አምስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰማኒያ አምስት ሺ አንድ መቶ ስልሳ ሶስት ብር ፤እና ሌሎች ሀገራት ገንዘብ ጨምሮ በድምሩ በእለቱ ምንዛሪ 8 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ከሀገር ሊወጣ ሲል ተይዟል፡፡rnrnገንዘቡን ሲያዘዋውሩ የነበሩ ሁለት ግለሰቦችም በቁጥጥር ስር ዉለዋል፡፡rnrnየገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አዳነች አቤቤ  የግል ጥቅማቸዉ ሳያስቀድሙ እና የኮንትሮባዲስቶች ድለላ ሳይበግራቸዉ ለሀገራቸው ሌት ተቀን እየሰሩ ለሚገኙት የቶጎጫሌ ጉሙሩክ ሰራተኞች እና አመራሮች  አድናቆታቸዉን  መግለጻቸዉን ከሚኒስቴሩ ያገኘነዉ መረጃ ያመለክታል፡፡

More in Economy