ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የኔዘርላንድስ ንግስት ማክስሲማንን ተቀብለው አነጋገሩ፡፡rnንግስቷ አካታች የሆነ የፋይናንስ ስርዐት እንዲጎለብት ለሚያደርጉት ጥረት ምስጋና ያቀረቡት ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ፤ አካታች የፋይናንስ ስርዐትን እውን ማድረግ የሚኖረው ፋይዳ በሌሎችም ዘርፎች ላይ በጉልህ የሚንጸባረቅ ነው ብለዋል፡፡rnበተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሃፊ የአካታች ፋይናንስ ልማት አምባሳደርነታቸው በኢትዮጵያ የሁለት ቀናት ጉብኝት በማድረግ ላይ የሚገኙት ንግስት ማክስሲማን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ዘርፉን ለማጎልበት የምታከናውናቸውን ተግባራት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር መወያየታቸውን ነው የተናገሩት፡፡rnrnአሁንም ግን ውጤታማ የሆነ አካታች የፋይናንስ ስርዓት ለመዘርጋት የሚደረገው ጥረት በተለይም ሴቶችን ያቀፈ ማድረግ እንደሚገባና ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ተግባራት በለየ መንገድ መሰራት እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡
← NewsPolitics
ፕሬዝደንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የኔዘርላንድስ ንግስት ማክስሲማንን ተቀብለው አነጋገሩ፡፡
Arts TV · ሜይ 15 2019




