በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎች እየተካሄዱ ነውrnrnበሰሜን ሸዋ፣ ኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ ምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ራያ ቆቦና ሌሎችም አካባቢዎች ሲከሰቱ የቆዩ የፀጥታ መደፍረሶችና በተለይ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ከሰሞኑ የተቀሰቀሰው ግጭት ያስከተለው ሞትና መፈናቀል ለሰልፎቹ መጠራት ምክንያት እንደሆኑ ታውቋል።rnrnበሠላማዊ ሠልፈኞቹ ‹‹በአማራ ብሔር ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ይቁም፤ መንግሥት የዜጎችን ደህንነት ይጠብቅ›› የሚሉና የተለያዩ መልዕክቶች እየተላለፉ ነው።rnrnየአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት እንደገለጸዉ ሰላማዊ ሰልፉ በደብረ ታቦር፣ ባህር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ማርቆስ፣ መርዓዊና በሌሎች ከተሞች እየተካሄደ ይገኛል።





