Arts TVArts TV
← NewsSport

በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት የተካሄዱ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መልካም ውጤት አስመዝግበዋል::

Arts TV · ሜይ 20 2019

በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት የተካሄዱ ውድድሮች ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች መልካም ውጤት አስመዝግበዋል::
ቅዳሜ ዕለት በተካሄደ የሻንጋይ የዲያመንድ ሊግ ውድድር ፡-rnrnወንዶች የ5000 ሜትር ርቀት ኢትዮጵያውያኑ ተከታትለው በመግባት አሸናፊ ሆነዋል፡፡ rn
    rn
  1. ዮሚፍ ቀጀልቻ… በ13:04.16
  2. rn
  3. ሰለሞን ባረጋ… በ13:04.71
  4. rn
  5. ሃጎስ ገ/ህይወት… 13:04.83
  6. rn
rnበሴቶች 1500 ሜትር ውድድር ደግሞ  rn
    rn
  1. ራባቢ አራፊ… በ4፡01.15 (ሞሮኮ)
  2. rn
  3. ጉዳፍ ፀጋዬ… በ4:01.25
  4. rn
  5. ዊኒ ናንዮንዶ… በ4፡01.39 (ኡጋንዳ)
  6. rn
  7. ዳዊት ስዩም… በ4:01.40 … በመሆን ሲጨርሱ አክሱማዊት እምባዬ 6ኛ እና አልማዝ ሳሙኤል 8 ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል፡፡ 3000 ሜትር መሠናክል ሴቶች የተወዳደረችው ወይንእሸት አንሳ 11ኛ ደረጃ ላይ ጨርሳለች፡፡
  8. rn
rnትናንት በተካሄዱ ሌሎች ውድድሮች፤ ላቲቪያ ላይ በተካሄደው የሪጋ ማራቶን በወንዶች አንዷለም በላይ ኬንያውያን አትሌቶችን በማስከተል በ2፡08.51 ሲያሸንፍ፤ ኢትዮጵያውያን የበላይ በሆኑበት የሴቶች ውድድር ደግሞ ብርቄ ደበሌ በ2፡26.18 ቀዳሚ ስትሆን፣ ወርቅነሽ አለሙ በ2፡27.30 ሁለተኛ እና ቁመሺ ሲቻሌ በ2፡29.44 ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ ጨርሰዋል፡፡rnrnrnrnበዴንማርክ መዲና የኮፐንሀገን ማራቶን በሴቶች እታለማሁ ዘለቀ በ2፡29.29 አንደኛ፤ ድንቅነሽ መካሽ በ2፡30.22 ሁለተኛ፣ አበሩ አያና በ2፡34.39 ሶስተኛ እንዲሁም ንግስት ሙሉነህ አራተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል፡፡ በወንዶች ገብሬ ሮባ ሶስተኛ ሆኗል፡፡rnrnበኔዘርላንድስ የሌይደን ማራቶን ደግሞ በሁለቱም ፆታ ኢትጵያውያን አትሌቶች ድል ሲያደርጉ፤ አለማየሁ መኮነን እና ደገፋ ዮሃንስ እንዲሁም በሴቶች ዘነቡ ፋንታዬ እና ቤንቱ ሽፈራው አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃን ይዘው አሸናፊ መሆን ችለዋል፡፡rnrnበኦስትሪያ ሳልዝበርግ ጋዲሴ ጉዲሳ በ2፡46. 37 አሸንፋለች፡፡rnrnጣሊያን ላይ የሜዛ ዴል ናቪግሊዮ ማራቶን በሴቶች አዲሳለም በላይ፣ አስመራወርቅ በላይ ተከታትለው በመግባት ባለድል ሆነዋል፡፡rnrnበህንድ ቤንጋሉሩ 10 ኪ.ሜ አንዱአምላክ በልሁ በ27፡56 ጊዜ ቀዳሚ ሲሆን ብርሃኑ ለገሰ በ28፡23 ሶስተኛ ወጥቷል፤ በሴቶች ደግሞ አኜስ ቲሮፕ ከኬንያ፤ ለተሰንበት ግደይ እና ሰንበሬ ተፈሪ ከኢትዮጵያ በ33፡55 ጊዜ በማይክሮ ሰከንዶች ተቀዳድመው 1ኛ፣ 2ኛ እና 3ኛ ሲወጡ እንዲሁም ሌሎች ኢትዮጵያውያኑ ነፃነት ጉደታ፣ ደራ ዲዳ እና ፀሃይ ገመቹ ከ4ኛ እስከ 6ኛ ያለውን ደረጃ ተቆናጥጠዋል፡፡ rnrn rnrnምንጭ፡ አፍሪካን አትሌቲክስ ዩናይትድ

More in Sport