Arts TVArts TV
← NewsEconomy

ለሀገራችን ኢንዱስትሪ ውጤታማነት በዘርፉ ያሉ ችግሮችን ተቀናጅቶ መፍታት ይገባል ተባለ

Arts TV · ኤፕሪ 1 2019

ለሀገራችን ኢንዱስትሪ ውጤታማነት በዘርፉ ያሉ ችግሮችን ተቀናጅቶ መፍታት ይገባል ተባለrnለሀገራችን ኢንዱስሪ ውጤማነት አነስተኛና መካከለኛ ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎቸ ያሉባቸውን ችግሮች ተቀናጅቶ መፍታት ይገባሉ ሲሉ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገ/እግዚአብሔር ተናገሩrnሚኒስትሯ ይህንን ያሉት ከፌዴራል አነስተኛና መካከለኛ ማኒፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ስትሪንግ ኮሚቴ ጋር  በኢንተርኮንቲነንታል ሆቴል በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡rnስትሪንግ ኮሚቴው አነስተኛና መካከለኛ ማኒፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች ውጤታማ እንዳይሆኑ ባደረጓቸው ችግሮች፣በዘርፉ በተሰሩ ስራዎችና ያሉ ችግሮች እንዲሁም በመፍትሄ አምጪ ጉዳዮች ላይ መክሯል፡፡rnrnየሀገሪቷን ኢኮኖሚ ከግብርና መር ወደ ኢንዱስትሪ መር ለማሸጋገር በሚደረገው ጥረት ኢንዱስትሪው የሚፈልገውን ውጤት እንዳላመጣ የተገመገመ ሲሆን ለዚህም የዳረጉት የአደረጃጀት፣የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ፣ የፋይናንስ አጠቃቀም እና የሼዶች በአግባቡ ስራ ላይ አለመዋል መሆናቸው በውይይቱ ተጠቅሰዋል፡፡rnrnወ/ሮ ፈትለወርቅ ችግሮቹን ለመፍታት ዘርፉን ለመደገፍ የተቋቋሙ ተቋማት፣ ክልሎች እና ድርሻ ያላቸው ድርጅቶች ተቀናጅው መስራት አለባቸው ብለዋል፡፡rnrnበፌዴራል ደረጃ የሚደረገው ድጋፍ እንደተጠበቀ ሆኖ የክልሎች ሚና ከፍተኛ ስለሆነ ሊያሰራቸው የሚችለውን አደረጃጀት በመፍጠር ከባለድርሻዎች ጋር ተቀራርቦ መስራት ይኖርባቸዋል ያሉት ሚኒስትሯ በካፒታል እቃዎች ግዥ መጓተት አምራቾችን ከሚደርስባችው አላስፈላጊ ወጪ ለመታደግ እና የውጪ ምንዛሪ ችግርንም ለማቃለል በሀገር ውስጥ የሚመረቱ ማሽኖችንና ግብዓቶችን በመጠቀም ከውጪ የምናስገባቸውን ማሽኖችን መጠን መቀነስ ይገባልም ብለዋል፡፡

More in Economy